የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ዋና ጸሃፊ አቶ በቀለ ነጋ ከቤታቸው እንዳይወጡ ተደርገዋል

  • እስክንድር ፍሬው

መረራ ጉዲና በኦሮምያ ክልል ለተቃውሞ ሰልፍ የወጡ የመድረክ ተሳታፊዎች ንግግር በሚያደርጉበት ጊዜ የተነሳ ፎቶ እአአ 2010 [ፋይል ፎቶ ሮይተርስ]

መንግስት በኛ ድርጅት ላይ ተጽዕኖ ለማድረግ የሚያስችሉትን እርምጃዎች እየወሰደ ነው ሲሉም የኦፌኮ ሊቀ-መንበር ዶክተር መራራ ጉዲና ተናግረዋል።

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ዋና ጸሃፊ አቶ በቀለ ነጋ ከቤታቸው እንዳይወጡ ተደርገዋል። ተንቀሳቃሽ ስልካቸውንም ተነጥቀዋል ሲሉ የፓርቲው ሊቀ-መንበር አስታወቁ።

መንግስት በኛ ድርጅት ላይ ተጽዕኖ ለማድረግ የሚያስችሉትን እርምጃዎች እየወሰደ ነው ሲሉም የኦፌኮ ሊቀ-መንበር ዶክተር መራራ ጉዲና ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ደግሞ በህጋዊ መንገድ ተመዝግበው በሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ውስጥ የሚገኙ ሰዎች ጭምር ሁከት እንዳስነሱና እንደመሩ ማስረጃ አለን ሲሉ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ሰሞኑን መናገራቸው ይታወቃል።

ዘጋብያችን እስክንደር ፍሬው ከአዲስ አበባ የላከው ዘገባ ዝርዝሩን አጠናቅሮ አቅርቦታል። ከዚህ በታች ካለው የድምፅ ፋይል በመጫን ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ዋና ጸሃፊ አቶ በቀለ ነጋ ከቤታቸው እንዳይወጡ ተደርገዋል