መቐለ ዩኒቨርሲቲ ለሰር ቦብ ጌልዶፍ የክብር ዶክትሬት ሰጠ

  • ግርማይ ገብሩ

መቐለ ዩኒቨርሲቲ ለሰር ቦብ ጌልዶፍ የክብር ዶክትሬት ሰጠ

የኢትዮጵያ ህዝብ ከ31 ዓመታት በፊት ባጋጣመው ከባድ ድርቅና ረሃብ ከህዝቡ ጎን በመቆም ከታደግዋቸው ምግባረ ሰናይ ሰዎች አንዱ ሰር ቦብ ጌልዶፍ እንደሆነ ይታወቃል።

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ለሰር ቦብ ጌልዶፍ የክብር ዶክትሬት መስጠቱን የሚገልፅ ስነ ስርዓት ትናንት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ተከናውኗል።

የኢትዮጵያ ህዝብ ከ31 ዓመታት በፊት ባጋጣመው ከባድ ድርቅና ረሃብ ከህዝቡ ጎን በመቆም ከታደግዋቸው ምግባረ ሰናይ ሰዎች አንዱ ሰር ቦብ ጌልዶፍ እንደሆነ ይታወቃል።

ከዚህም በመነሳት ሰር ቦብ ጌልዶፍ በዚያን ጊዜ ላበረከተው ሰብአዊ ተግባርና ዛሬም ድረስ ኢትዮጵያ ውስጥ እያደረገ ላለው የልማት እንቅስቃሴ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት መስጠቱን በዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶክተር ክንደያ ገብረህይወት በበኩሉ ገልጿል።

ሰር ቦብ ጌልዶፍም በተካሄደለት ዝግጅት በአካል ተገኝቶ ጥልቅ ደስታውን ገልጿል።

Your browser doesn’t support HTML5

መቐለ ዩኒቨርሲቲ ለሰር ቦብ ጌልዶፍ የክብር ዶክትሬት ሰጠ