በባለሥልጣናትና የሃገር ውስጥ ዜና ዘገባዎች መሠረት፥ ዛሬ ምዕራብ ሊቢያ ውስጥ ግዙፍ ፈንጅ የተጠመደበት መኪና በአንድ የፖሊሶች ማሰልጠኛ ማዕከል ላይ ባደረሰው ጥቃት፥ በትንሹ ለ50 ሰዎች መገደልና ለሌሎች በርካቶች መጎዳት ምክንያት ሆኗል።
ቦምቡ የፈነዳው ዚሊተን(Zliten) ከተማ ውስጥ በሚገኘው ማዕከል በመቶዎች የሚገመቱ ምልምሎች በተሰበሰቡበት ወቅት ነው።
በጥቃቱ የሞቱት ሰዎች 50 መሆናቸውን የዜና ዘገባዎች ቢገልጹም፥ የሆስፒታል ምንጮች ግን የሰለባዎቹን ቁጥር 65 ያደርሱታል።
ለጥቃቱ እስካሁን ኃላፊነቱን የወሰደ የለም።
በሊቢያ የተባበሩት መንግሥታት ተልዕኮ አስተባባሪ ማርቲን ኮብለር (Martin Kobler) በትዊተር (Twitter) መልዕክታቸው፥ ”ጥቃቱ በአጥፍቶ ጠፊ የተፈጸመ ነው” ሲሉ አውግዘው፥ ሊብያውያን ባስቸኳይ ተባብረው አሸባሪነትን እንዲዋጉ ጥሪ አስተላልፈዋል።
I condemn in the strongest terms today%27s deadly suicide attack in Zliten, call on all Libyans to urgently unite in fight against terrorism
— Martin Kobler (@KoblerSRSG) January 7, 2016
I condemn in the strongest terms today%27s deadly suicide attack in Zliten, call on all Libyans to urgently unite in fight against terrorism
— Martin Kobler (@KoblerSRSG) January 7, 2016
I call on all Libyans to unite behind the Gov. of National Accord (GNA) so that together they can eliminate the threat of Daesh
— Martin Kobler (@KoblerSRSG) January 5, 2016
ሊቢያ ባሁኑ ወቅት፥ ትሪፖሊ(Tripoli)ን በሚቆጣጠረው እስላማዊ አስተዳደርና ዓለምአቀፍ እውቅና ባገኘውና ወደ ምሥራቅ ቶብሩክ(Tobruk) በሸሸው ፓርላማ ተከፍላለች።
የዜና ዘገባ አለን የድምጽ ፋይሉን በመጫን ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5