ዊልያም ሩቶ በአይ ሲ ሲ የተሰጠው ብይን ከቀረበብኝ ክስ ነፃ መሆኔን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል  

  • ሰሎሞን ክፍሌ

ፋይል - ምክትል ፕሬዘዳንት ዊልያም ሩቶ ከእናታቸውና ከባለቤታቸው ጋር /ፎቶ ሮይተርስ/

ምክትል ፕሬዘዳንቱ ዊልያም ሩቶ እና የአንድ ያካባቢው ራዲዮ ጣቢያ ዲሬክተር፥ እጃቸው አለበት ተብሎ የቀረበባቸውን ክስ በዚህ ሣምንት ውድቅ መደረጉ ይታወሳል።

ዓለም አቀፉ የወንጀል ችሎት በኬንያ እ .አ. አ. በ 2007 - 2008 ዓ.ም. የተካሄደውን ምርጫ ተከትሎ በተቀሰቀሰው ሁከት ምክትል ፕሬዘዳንቱ ዊልያም ሩቶ እና የአንድ ያካባቢው ራዲዮ ጣቢያ ዲሬክተር፥ እጃቸው አለበት ተብሎ የቀረበባቸውን ክስ በዚህ ሣምንት ውድቅ አድርጓል።

ሩቶ ዛሬ ናይሮቢ ውስጥ ለጋዜጠኞች ሲናገሩ፥ የተሰጠው ብይን ከቀረበብኝ ክስ ነፃ መሆኔን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።

ከናይሮቢ ለኒ ሩቫጋ የላከውን ዘገባ፣ ሰሎሞን ክፍሌ አቅርቦታል። ከድምጽ ፋይሉ ያድምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ዊልያም ሩቶ በአይ ሲ ሲ የተሰጠው ብይን ከቀረበብኝ ክስ ነፃ መሆኔን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል