በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አፍሪካዊያን ከአይሲሲ በደቦ ወሙጣታቸውን ኢትዮጵያ ትደግፋለች


በዓለምአቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ተከስሰው ጉዳያቸው እየታየ ያለው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታና ምክትል ፕሬዚዳንቱ ዊልያም ሩቶ /የተከሰሱባቸው ‘አቀናብረዋቸዋል’ ወይም ‘ተሣትፈውባቸዋል’ ተብለው የተጠረጠሩባቸው ‘በሰብዕና ላይ የተደረጉ ወንጀሎች’ የተፈፀሙት እንደስማቸው ቅደም ተከተል የኬንያ የገንዘብ ሚኒስትርና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር በነበሩበት እአአ በ2007 ዓ.ም ነው፡፡
በዓለምአቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ተከስሰው ጉዳያቸው እየታየ ያለው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታና ምክትል ፕሬዚዳንቱ ዊልያም ሩቶ /የተከሰሱባቸው ‘አቀናብረዋቸዋል’ ወይም ‘ተሣትፈውባቸዋል’ ተብለው የተጠረጠሩባቸው ‘በሰብዕና ላይ የተደረጉ ወንጀሎች’ የተፈፀሙት እንደስማቸው ቅደም ተከተል የኬንያ የገንዘብ ሚኒስትርና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር በነበሩበት እአአ በ2007 ዓ.ም ነው፡፡

የአፍሪካ ሃገሮች ከዓለምአቀፉ የወንጀል ችሎት - አይሲሲ አባልነት በደቦ እንዲወጡ ለማድረግ ኬንያ የጀመረችውን ጥረት እንደምትደግፍ የአፍሪካ ኅብረት የወቅቱ ሊቀመንበር ኢትዮጵያ አስታውቃለች፡፡





ዓለምአቀፍ የወንጀል ችሎት - አይሲሲ
ዓለምአቀፍ የወንጀል ችሎት - አይሲሲ

please wait

No media source currently available

0:00 0:07:29 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ


የአፍሪካ ሃገሮች ከዓለምአቀፉ የወንጀል ችሎት - አይሲሲ አባልነት በደቦ እንዲወጡ ለማድረግ ኬንያ የጀመረችውን ጥረት እንደምትደግፍ የአፍሪካ ኅብረት የወቅቱ ሊቀመንበር ኢትዮጵያ አስታውቃለች፡፡

ዓለምአቀፉ የወንጀል ችሎት በኬንያው ምክትል ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ላይ በሰብዕና ላይ በተፈፀሙ ወንጀሎች ክሥ መሥርቶ ጉዳያቸው ጄኔቫ ላይ እየታየ ሲሆን ፕሬዚዳንቱ ኡሁሩ ኬንያታ ደግሞ የፊታችን ኅዳር እንደሚቀርቡ ታውቋል፡፡
የአፍሪካ ሕብረት
የአፍሪካ ሕብረት

የአፍሪካ ኅብረት በመጭው ወር ውስጥ በዚሁ የኬንያ ባለሥልጣናት ክሥና የፍርድ ሂደት ጉዳይ ላይ ልዩ ስብሰባ እንደሚያካሂድ የኅብረቱ ሥራ አስፈፃሚ አካል ምክትል ኃላፊ የሆኑት ኬንያዊው ኤራስቱስ ሞኤንቻ ለፈረንሣዩ የዜና ወኪል ገልፀዋል፡፡

ጉዳያቸው በዓለምአቀፉ የወንጀል ችሎት በተያዘው ከፍተኞቹ የኬንያ ባለሥልጣናት የፍርድ ሂደት ጉዳይ ላይ ኬንያዊያን የተለያየ አስተያየት አላቸው፡፡
በአይሲሲ እየታደኑ ያሉት ኦማር ሁሴን አል-በሽር - የሱዳን ፕሬዚዳንት
በአይሲሲ እየታደኑ ያሉት ኦማር ሁሴን አል-በሽር - የሱዳን ፕሬዚዳንት

በሌላ በኩል ደግሞ ዩናይትድ ስቴትስ የሱዳኑን ፕሬዚዳንት ኦማር ሁሴን አል በሽርን የመግቢያ ቪዛ ጥያቄ እያጠናች መሆኗን ገልፃለች፡፡

ለዝርዝር ዘገባው የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
XS
SM
MD
LG