የሩሲያ ወታደሮች ወደ ዩክሬን ዋና ከተማ ኪየቭ እያመሩ ነው

Your browser doesn’t support HTML5

የሩሲያ ወታደሮች በሁሉም አቅጣጫ ወደ ዩክሬን መግባታቸውንና ወደ ዋና ከተማዋ ኪየቭ እያመሩ መሆኑን በሥፍራው የምትገኘው የአሜሪካ ድምፅ ዘጋቢ ሄዘር መርዶክ በቪዲዮ በላከችው ዘገባ አስታውቃለች።

የዩክሬን ነዋሪዎች ለደህንነታቸው ወዴት መሄድ እናዳለባቸውና ቀጥሎ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ባለማወቅ ግራ መጋባት ላይ መሆናቸውንና ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ከ10 ሰዎች በላይ ንፁሃን ዜጎች እንዲሁም በርካታ ወታደሮች መገደላቸውን ገልጻለች።

ሄዘር ከከርኪቭ ወደ ኪየቭ በመኪና እየተጓዘች የላከችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይመልከቱ።