የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሺን የኦሮምያና የአማራን ሪፖርቶች ሊያቀርብ ነው

  • እስክንድር ፍሬው

ፋይል ፎቶ - በኦሮሚያ በሰላማዊ ሰልፍ ወቅት የተገደለ ወጣት የቀብር ሥነ-ስርዓት የተሳተፉ ሃዘንተኛ

በኦሮምያና በአማራ ክልሎች ተፈፅመዋል የተባሉ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን የተመለከተ ሪፖርት ከሁለት ሣምንታት በኋላ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርብ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሺን አስታወቀ።

በኦሮምያና በአማራ ክልሎች ተፈፅመዋል የተባሉ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን የተመለከተ ሪፖርት ከሁለት ሣምንታት በኋላ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርብ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሺን አስታወቀ።

ኮሚሺኑ ያጣራው በሁለቱ ክልሎች ከተከሰቱ ግጭቶች ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን መሆኑን ኮሚሺነር አዲሱ ገብረ እግዚአብሄር ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሺን በመንግሥት የተቋቋመና ለመንግሥት የሚያደላ ተቋም ነው ሲሉ ተቃዋሚዎች ይተቻሉ።

ለተጨማሪ የእስክንድር ፍሬውን የአዲስ አበባ ዘገባ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሺን የኦሮምያና የአማራን ሪፖርቶች ሊያቀርብ ነው

Your browser doesn’t support HTML5

የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሺን የኦሮምያና የአማራን ሪፖርቶች ሊያቀርብ ነው - 2