ከአዲስ አበባ ተነስቶ ወደ ኬንያ-ናይሮቢ በረራ ላይ እንዳለ ከወደቀው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አይሮፕላን ተሣፋሪዎች በህይወት የተረፈ አለመኖሩ ተገልጿል። የአሜሪካ ኤምባሲ ኀዘኑን ገልጿል።
አዲስ አበባ —
ቢሾፍቱ አካባቢ በወደቀው አይሮፕላን ውስጥ ተሣፍረው የነበሩት 157 ሰዎች ሲሆኑ 149 መንገደኞችና ስምንቱ የበረራ ሠራተኞች ነበሩ።
አይሮፕላኑ የወደቀበት ሥፍራ ላይ ዛሬ ተገኝተው የተመለከቱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የአደጋው መንስዔ እንዲጣራ ለሟች ቤተሰቦችም ተገቢው ሁሉ እንዲደረግ መመሪያ ሰጥተዋል።
PM Abiy Ahmed shared his condolences in a televised address on behalf of the FDRE Government. The House of People’s Representatives have declared March 11, 2019 a national day of mourning for citizens of all countries that have passed in this tragic accident. #PMOEthiopia pic.twitter.com/F0aA1sPnYP
— Office of the Prime Minister - Ethiopia (@PMEthiopia) March 10, 2019
ለተጎጂዎች ሁሉ የኀዘን መግለጫ መልዕክት ያስተላለፈው በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ በአደጋው የሞቱ አሜሪካዊያንን ለመለየት እየሠራ መሆኑን አስታውቋል።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5