Your browser doesn’t support HTML5
“ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዐት ያነሳ እስከጠዋት ባሕሩ ውስጥ ነበርን” ጅቡቲ ጠረፍ ላይ ከደረሰው አደጋ በህይወት የተረፉ
ባለፈው ሰኞ በጀልባ ተሳፍረው ከየመን ወደ ጅቡቲ በመጓዝ ላይ ሳሉ ባጋጠማቸው ችግር የተነሳ ለህልፈት የተዳረጉ ከአደጋው በሕይወት የተረፉ እንዲሁም የት እንደደረሱ ያልታወቀ ፍልሰተኞችን በሚመለከት ባለፈው ዓርብ መዘገባችን ይታወሳል፡፡
SEE ALSO: በጂቡቲ ባሕር ዳርቻ የሰጠሙት ፍልሰተኞች ሕገወጥ አስተላላፊዎች ከጀልባው እንዲወርዱ በማስገደዳቸው ነው - አይኦኤምከተከሰተው አደጋ በሕይወት ተርፈው ጅቡቲ ውስጥ "ሀዩ" በምትባል ቦታ ከተጠለሉት መካከል የኦፋን ኦሮሞ ባልደረባችን ጃለኔ ገመዳ አንዱን አነጋግራለች፡፡ ስሙን እንዳይገለጥ ጠይቆ ስለአደጋው እንደሚከተለው ገልጾላታል፡፡