አክራሪ ቡድን የለቀቃቸው የቀድሞዋ ታጋች በቡርኪና ፋሦ ዋና ከተማ ኡጋዱጉ ገብተዋል

  • ሰሎሞን ክፍሌ

የአውስትራልያ ዜጋ የሆኑትን ጆይስሊን ኤልየት ከቡርኪና ፋሦ ፕረዚደንት ጋር

የአውስትራልያ ዜጋ የሆኑትን ጆይስሊን ኤልየት በያዝነው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ቡርኪና ፋሦ ዋና ከተማ ኡጋዱጉ ገብተዋል። ​

የቀድሞዋ ታጋች ጆይስሊን ኤልየት ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት ያለው አክራሪ ቡድን ከለቀቃቸው ሁለት ቀናት በኋላ፥ በያዝነው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ቡርኪና ፋሦ ዋና ከተማ ኡጋዱጉ ገብተዋል። ​

አሸባሪው ቡድን የአውስትራልያ ዜጋ የሆኑትን ሴትና ባለቤታቸውን ከሦስት ሳምንታት በፊት የጠለፈው ራቅ ብሎ ከሚገኝ መንደር ውስጥ እንደነበር ይታወሳል።

ጆይስሊን ኤልየት​ለመገናኛ ብዙሃን ሲናገሩ፥ ባለቤታቸውን ለማስለቀቅ በጀመሩት እንደሚቀጥሉና ሀገሪቱ ውስጥ መሥራታቸውን እንደማያቆሙ አስረድተዋል።

ባልደረባችን ኤምሊ ሎብ ከአቢጃን ያደረሰችን አጭር ዘገባ አለ። ሰሎሞን ክፍሌ አቅርቦታል ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

አክራሪ ቡድን የለቀቃቸው የቀድሞዋ ታጋች በቡርኪና ፋሦ ዋና ከተማ ኡጋዱጉ ገብተዋል