በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በየመን የአየር ድብደባ ሰዎች ተገደሉ


የየመን መንግሥትን የሚደግፈው በሳዑዲ ዓረብያ የሚመራው የጥምረት ኃይል ዛሬ ሰንዓ ላይ ተከትታይ የአየር ድብደባዎች ማካሄዱ ታውቋል። ቢያንስ ሥድስት ሰዎች እንደተገደሉ ተዘግቧል።

የአየር ድብደባው በከተማይቱ የተለያዩ ዒላማዎችን በመምታቱ በርካታ ቤቶች ተደርምሰዋል።

ሰንዓ ለአምስት ዓመታት ያህል በኢራን በሚደገፉት የሁቲ አማጽያን ቁጥጥር ሥር ቆይታለች። የዛሬው የአየር ድብደባ የተካሄደው በሳዑዲ ዓረብያ የነዳጅ ዘይት መተላለፊያ ቱቦ ላይ በተፈፀመው የድሮን ማለት “የሰው አልባ” ተዋጊ አውሮፕላን ጥቃት የሁቲ አማጽያን ኃላፊነት ከወሰድ ጥቂት ቀናት በኋላ ነው።

የሳዑዲ ምክትል የመከላከይ ሚኒስትር ኻሊድ ቢን ሳልመን በነዳጅ ዘይት መተላለፍያ ቱባ ላይ የተካሄደውን ጥቃት ያዘዘችው ኢራን ናት ሲሉ ከሰዋል። የአሸባሪነት ተግባር ነውም ብለዋታል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG