በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ወሎ ዩኒቨርሲቲ ስለደረሰበት ጉዳት


በጦርነቱ ጉዳት የደረሰበት የወሎ ዩኒቨርስቲ ከፊል ገፅታ
በጦርነቱ ጉዳት የደረሰበት የወሎ ዩኒቨርስቲ ከፊል ገፅታ

የህወሓት ታጣቂዎች በወሎ ዩኒቨርሲቲ ላይ አደረሱ የተባለው ጉዳት 15 ቢሊዮን ብር እንደሚገመት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ገልፀዋል።

ፕሬዚደንቱ በአካባቢው ጦርነት ባልነበረበት ወቅት ተዋጊዎቹ ዩኒቨርሲቲው ላይ ከባድ መሣሪያዎችን እንደተኮሱና በወቅቱ እርሳቸውም ቢሯቸው ውስጥ እንደነበሩ ተናግረዋል።

በመቀጠልም የዩኒቨርሲቲውን በርካታ ቁሳቁስና ንብረት ዘርፈው መወሰዳቸውንም የገለፁ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪዎችም ይህንኑ መስክረዋል።

ትግራይ ክልልን በማስተዳደር ላይ የሚገኙት ባለሥልጣናትና የህወሓት መሪዎች ለዚህ ክስ በቀጥታ ምላሽ ባይሰጡም ከዚህ ቀደም መሰል ክሦችን ሲያስተባብሉ መቆየታቸው ይታወቃል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያገኛሉ።

ወሎ ዩኒቨርሲቲ ስለደረሰበት ጉዳት
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:14 0:00


XS
SM
MD
LG