በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አስቸኳይ የገንዘብ እርዳታ ለሱዳን


ኻርቱም
ኻርቱም

ሱዳን የተጋፈጠችውን የገንዘብ ቀውስ ለማቅለል ይውላል የተባለ አንድ ቢሊዮን ተኩል ዶላር አዋጥተው እንደሚለግሱ ምዕራባውያን አረብ ሃገሮች ቃል ገቡ።

ከጀርመን በርሊን በርቀት በኢንተርኔት አማካይነት የተነጋገረው ጉባዔ የተጠራው የሱዳን የሽግግር መንግሥት ወደ ዴሞክራሲ እንዲያመራ ለመርዳት መሆኑ ተገልጿል።

የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር ሃገራቸው ከባድ ችግር ላይ መሆኗን ገልፀው ዓለምአቀፍ ርዳታ እንዲደርስላቸው ተማፅነዋል።

“ሱዳንን መርዳት የቸርነት ጉዳይ ሳይሆን ዓለም ዴሞክራሲያዊትና የተረጋጋች ሱዳንን ስለሚፈልግ ነው” ብለዋል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶንዮ ጉቴሬዥ።

XS
SM
MD
LG