ሩሲያ በዩክሬን ሲቪሎች ላይ የምታደርሰው ጥቃት ከፍ ብሏል
/ማሳሰቢያ በዚህ ዘገባ ውስጥ አንዳንድ ተመልካቾች አዋኪ ሆነው የሚያገኟቸው ምስሎች ሊኖሩ ይችላሉ/ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ሩሲያ ያለ አንዳች ቆስቋሽ ምክኒያት በአገራቸው ላይ የከፈተችው ጦርነት መላውን አውሮፓ አደጋ ላይ የሚጥል “ውደመት ነው” አሉ። ሁለተኛ ወሩን በያዘው ጦርነት፣ የዩክሬይኗን ዋና ከተማ ኪየቭን ከእጁ ለማስገባት የሩሲያ ጦር አቅዶት የነበረውን ውጥኑን የተወ ይመስላል። ይሁን እንጂ ምዕራባውያን ኃያላን ከነበሩበት ወታደራዊ ይዞታ በማፈግፈግ ላይ ያሉትን የሩሲያ ወታደሮች አስገድዶ መድፈር እና በሰላማዊ ሰዎች ላይ በርሸና መልክ ተፈጽመዋል የተባሉ ግድያዎችን ጨምሮ በጦር ወንጀለኝነት ይከሳሉ።