በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በዋግኽምራ ዞን 15 ሕፃናት በኩፍኝ ወረርሽኝ ሕይወታቸው ማለፉን ጽሕፈት ቤቱ አስታወቀ


የኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ

በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን መደበኛ ክትባት በመቋረጡ በተከሠተው የኩፍኝ ወረርሽ፣ ባለፈው ወር ብቻ 15 ሕፃናት መሞታቸውን፣ የዞኑ ጤና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

 በዋግኽምራ ዞን 15 ሕፃናት በኩፍኝ ወረርሽኝ ሕይወታቸው ማለፉን ጽሕፈት ቤቱ አስታወቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:50 0:00

የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ፣ ዛሬ ማክሰኞ ለአሜሪካ ድምፅ እንደገለጹት፣ በአካባቢው በተደጋጋሚ ባጋጠመው የጸጥታ ችግር የተነሣ ሕፃናት በዕድሜያቸው ማግኘት የነበረባቸውን መደበኛ ክትባት አላገኙም።

ከአምስት ወራት በፊት በሰሀላ ሰየምት ወረዳ ብቻ ተከሥቶ የነበረው የኩፍኝ ወረርሽኝ በኹሉም ወረዳዎች በመስፋፋቱ፣ በአሁኑ ሰዓት ሁለት ሺሕ ሕፃናት በወረርሽኙ መያዛቸውን ገልጸዋል።

የሰሜን ወሎ፣ አጎራባች ዞንና ክልሎች ተፈናቃዮች በደሴ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:13 0:00

በቅርቡ፣ ለሕፃናቱ በዘመቻ መልክ የክትባት አገልግሎት እንደሚጀመር የጠቆሙት ኃላፊው፣ በጸጥታው ችግር የተነሣ ለባለሞያዎች ተደራሽነት አዳጋች በኾኑ ወረዳዎች ያሉ ሕፃናትን ለመታደግም ረጂ ድርጅቶች ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG