የክራሯ ንግሥት አስኒ ስትታወስ
በቀደመው ዘመን፣ በዳንስ እና ውዝዋዜ፣ በልዩ ዝነጣ፣ እንዲሁም በክራር በታጀበ ሙዚቃዋ ነግሣ ኖራለች። በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ሴት የመድረክ ተዋናይትም ናት፤ አስናቀች ወርቁ። በዕድሜ ዘመንዋ መካተቻ ላይ ፣ እርሷን የሚዘክር “አስኒ” የተሰኘ ፊልም ተሠርቶ በቪሚዮ መተግበሪያ ላይ እየታየ ይገኛል። የ “አስኒ” ፊልም ዳይሬክተር እና ፕሮዲውሰር ሬቸል ሳሙኤል፣ ፊልሙ እንዴት እንደተሠራ፣ እንዲሁም አስኒ ስለነበራት ሰብእና ከአሜሪካ ድምፅ ጋራ ቆይታ አድርጋለች።