በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዩኤስአይዲ አስተዳዳሪ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ሊያደርጉ ነው


የዩናይትድ ስቴትስ ዓለምቀፍ የልማት ተራድዖ ድርጅት /ዩኤስአይዲ/ አስተዳዳሪ ማርክ ግሪን ከነገ ጀምሮ የሁለት ቀናት የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ ያደርጋሉ፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ ዓለምቀፍ የልማት ተራድዖ ድርጅት /ዩኤስአይዲ/ አስተዳዳሪ ማርክ ግሪን ከነገ ጀምሮ የሁለት ቀናት የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ ያደርጋሉ፡፡ አስተዳዳሪው የመጀመሪያ ለሆነ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙት 8.5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን በድርቅ ምክንያት ለዕርዳታ በተጋለጡበት ወቅት ነው፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ ዓለምቀፍ የልማት ተራድዖ ድርጅት /ዩኤስአይዲ/ አስተዳዳሪ ማርክ ግሪን ወደ አፍሪካ ብሎም ወደ ኢትዮጵያ ሲጓዚ የመጀመሪያቸው ነው፡፡ ጉብኝታቸውም በድርቅ ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ ዕርዳታ የሚያስፈልጋቸው የኢትዮጵያውያን ቁጥር መጨመሩ ይፋ ከተደረገበት ወቅት ጋራ ተገጣጥሟል፡፡

በድርጅታቸው የሚደገፉና የማኅበረሰቡን የተፈጥሮ አደጋ የመቋቋም ብቃት እንዲሁም የኢኮኖሚ አቅም የሚያጠናክሩ ፕሮጀክቶችን ይመለከታሉ፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

የዩኤስአይዲ አስተዳዳሪ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ሊያደርጉ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:45 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG