የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ለዩክሬን የሚሰጠው ወታደራዊ ድጋፍ እንዲቋረጥ ሰኞ ዕለት ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። ይህም ሁሉም ወገኖች ወደ ሰላም ንግግር እንዲገቡ ለማስገደድ የታለመ ርምጃ መሆኑን አስተዳደራቸው አስታውቋል።
የቪኦኤው ሄንሪ ሪጅዌል ከለንደን በላከው ዘገባ፣ የአውሮፓ መሪዎች በበኩላቸው ለዩክሬን መሣሪያ መላክ መቀጠሉ እጅግ አስፈላጊ እንደሆነ አስታውቀዋል። ዩክሬን እስከመቼ ውጊያውን መቀጠል እንደምትችል ግን እርግጠኞች አይደሉም።
መድረክ / ፎረም