የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ትላንት ሐሙስ ከህንድ ጠቅላይ ሚንስትር ኔራንድራ ሞዲ ጋራ በርከት ያሉ የኃይል ምንጭ (ኤነርጂ) እና የመከላከያ ስምምነቶች ተፈራርመዋል።
ሞዲ ፕሬዝደንት ትረምፕ ሁለተኛውን የሥልጣን ዘመናቸውን ከጀመሩ ወዲህ ኋይት ሃውስን ሲጎበኙ ይህ የመጀመሪያቸው ነው። ትረምፕ በአሜሪካ የንግድ አጋሮች ላይ አጸፋ ቀረጥ እንደሚጣል አመልክተዋል።
ህንድ ቀረጦቹን ለመከላከል ጥረት ስታደርግ መቆየቷን ጠቅሳ አኒታ ፓወል ከኋይት ሐውስ ያሰናዳችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
መድረክ / ፎረም