ዋሺንግተን ዲሲ —
ከሶማልያ መንግሥት ጋር የተቀነባበር የዩናይትድ ስቴትስ የአየር ድብደባ በርካታ የአል ሸባብ አመፅያንን እንደገደለ የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ዕዝ ያወጣው መግለጫ ጠቁሟል።
የትላንቱ የአየር ድብደባ የተካሄደው ከመዲናይቱ ሞቃዲሹ ሰሜን ምዕራብ 97 ኪሎሜትር ርቀት ባለው ቦታ ላይ መሆኑን ዕዙ ያወጣው መግለጫ ጠቅሷል።
አንዳንድ ባለሥልጣኖች እንደሚሉት አሁን በፅንፈኛው ቡድን ላይ በመካሄደ ላይ ያለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ሰፊ ጥቃት ለመክፈት ያመቻቻል።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ