የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ በብረታ ብረት እና አሉሚነም ላይ ትላንት ሰኞ የ25 ከመቶ ቀረጥ ጥለዋል።
በቀረጡ በጣም የሚጎዱት ለአሜሪካ ዋናዎቹ የብረታ ብረት እና አሉሚነም አቅራቢዎች የሆኑት ካናዳ እና ሜክሲኮ ሊሆኑ እንደሚችሉ ተመልክቷል። ትረምፕ ንግድን በሚመለከት እየወሰዱ ያሉት ርምጃ ከዋናዋ የዩናይትድ ስቴትስ ተቀናቃኝ ከቻይና በኩል የበረታ ነቀፌታ አስከትሏል።
የአሜሪካ ድምጽ የኋይት ሐውስ ዘጋቢ አኒታ ፓወል ያጠናቀረችው ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
መድረክ / ፎረም