በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ተመድ በሮሒንግያ ሙስሊሞች ስደት አስቸኳይ ስብሰባ ሊያካሂድ ነው


ምዕራባዊ ሚያንማር ውስጥ በተቀሰቀሰውና ወደ 4መቶ ሺህ የበሮሒንግያ ሙስሊሞች፣ ድንበር አቋርጠው ወደ ባንግላዴሽ እንዲሰደዱ ያስገደደውን ቀውስ በተመለከተ፣ የተመድ የፀጥታው ጥበቃ ምክር ቤት በዚህ ሳምንት ውስጥ አንድ አስቸኳይ ስብሰባ እንደሚያካሂድ ተገለጸ።

ምዕራባዊ ሚያንማር ውስጥ በተቀሰቀሰውና ወደ 4መቶ ሺህ የበሮሒንግያሙስሊሞች፣ ድንበር አቋርጠው ወደ ባንግላዴሽ እንዲሰደዱ ያስገደደውን ቀውስ በተመለከተ፣ የተመድ የፀጥታው ጥበቃ ምክር ቤት በዚህ ሳምንት ውስጥ አንድ አስቸኳይ ስብሰባ እንደሚያካሂድ ተገለጸ።

ለነገ ረቡዕ የተቀጠረው የምክር ቤቱ ስብሰባ እንዲጠራ የተጠየቀው በብሪታንያና በስዊድን ሲሆን፣ ይህም የተመድ የሰብዓዊ አገልግሎት ዋና ኃላፊ ዘይድ ራአድ አል ሁሴን ትናንት ሰኞ፣ ድርጊቱ የዘር ማፅዳት ምሳሌ መሆኑን ከገለፁ በኋላ ነው።

ተመድ በሮሒንግያ ሙስሊሞች ስደት አስቸኳይ ስብሰባ ሊያካሂድ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:43 0:00

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ሃላፊ ዘይድ ረአድ አል ሁሴን መንግሥታት ወደ አምባገንንነትና ወደ ጭቆና እንዲሁም ሰብዓዊ መብትን ወደ መርገጥ እያመሩ ናቸው ሲሉ ነበር ትናንት ያስጠነቀቁት።

የተመድ የሥደተኞች መሥራያ ቤት፣ አመፁ ከተቀሰቀሰበት ካለፈው ከነሐሴ 19 ወዲህ፣ ወደ 370,000 የሮሒንግያ ነዋሪዎች ወደ ባንግላዴሽ እንደተሰደዱ አመልክቶ፣ በተያያዘ ግጭትም 400 ያህል ሰዎች እንደሞቱ ገልጧል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG