በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሩሲያ 22 የዩክሬይን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ጥያለሁ አለች


የሩሲያ ወታደር የተማረከውን የዩክሬን ሰው አልባ ድሮን ይዞ ሥፍራው ባልተገለጸ ቦታ እአአ መጋቢት 25/2024
የሩሲያ ወታደር የተማረከውን የዩክሬን ሰው አልባ ድሮን ይዞ ሥፍራው ባልተገለጸ ቦታ እአአ መጋቢት 25/2024

የሩሲያ የመከላከያ ሚንስቴር የአየር ጥቃት መከላከያ ኅይሎቻችን የዩክሬይንን 22 ሰው አልባ አውሮፕላኖች ጥለዋል ሲል ተናገረ፡፡

አስራ አምስቱን ብሪያንስክ ፍለ ግዛት ስድስቱን ደግሞ በሩስያ ቁጥጥር ስር ባለችው ክራይሚያ እንዲሁም አንዱን ድሮን ሊፕትሴክ ውስጥ መጣሉን ነው ሚንስቴሩ ያስታወቀው፡፡

ኩርስክ በተባለው የዩክሬይን አዋሳኝ ግዛትም ሶስት ድሮኖች ተመትተው ወድቀዋል ሲሉ የክፍለ ግዛቷ አገረ ገዢ ተናግረዋል፡፡

የዩክሬይን የጦር ኅይል በበኩሉ ሩሲያ በበርካታ አካባቢዎች የአየር ጥቃት ታደርሳለች ሲል ዛሬ ማስጠንቀቁም ተመልክቷል፡፡ የድኒፕሮፐትሮቭስክ አገረ ገዢ በሰጡት ቃል ሩሲያ በድሮን እና በመድፍ ባደረሰችው ጥቃት በርካታ የመኖሪያ ቤቶች እንደወደሙ ገልጸዋል፡፡ በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት ግን እንደሌለ አስታውቀዋል፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG