በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዩናይትድ ስቴትስ የኢሚግሬሽን ሕግ ታሪክ


አሜሪካ ወደ ሃገርዋ የሚመጡ የውጭ ሃገር ሰዎች ላይ ገደብ ስታደርግ የመጀመሪያ ጊዜያዋ አይደለም፡፡ ታዲያ በዜግነታቸው እየለየች “አትምጡብኝ፡” ብላ ታውቃለች እንዴ? “እንዴታ!”

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው ሳምንት የፈረሙዋቸው የኢሚግሬሽን ማስፈፀሚያ ትዕዛዞች በቅርብ ዘመናት የአሜሪካ ታሪክ እንዲህ ያለ መመሪያ ሲወጣ የመጀመሪያ ሊሆን ይችላል። ዩናይትድ ስቴትስ በምትቀበላቸው የውጭ ሃገር ሰዎች ላይ ገደብ ስታደርግ ግን የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም።

እኤአ በ1789 ዓ.ም የተደነገገው የዩናይትድ ስቴትስ ሕገ መንግሥት የኢሚግሬሽን ሕግን ሙሉ ሥልጣን ለሀገሪቱ ለምክር ቤቱ ሰጡዋል።

ፕሬዚደንቱ ደግሞ ሕጎቹን በመመሪያዎች አማካይነት እየተቆጣጠረ ያስፈፅማል ይላሉ

“ዘ ወርድስ ዊ ሊቭ ባይ” በሚል ርዕስ ስለ ሕገ መንግሥቱ የሚያወሳ መፅሃፍ የደረሱት ሊንዳ ሞንክ።

በመጀመሪያዎቹ የአንድ መቶ ዓመታት የአሜሪካ ታሪክ ታዲያ ኮንግሬሱ በኢሚግሬሽን ሕጉ ላይ በፌዴራሉ መንግሥት ደረጃ ገደብ የሚጥል ደምብ አውጥቶ አያውቅም። ብዛት ያላቸው የአየርላንድ እና የጀርመን ተወላጆች ወደዩናትድ ስቴትስ ፈልሰው የሰፈሩትም በእነዚህ ዓመታት ነው።

ብዙዎች የቻይና ተወላጆችም በ1860ዎቹ ዓመታት በባቡር መሥመር ዝርጋታ ሥራ በወዛደርነት ሊሰሩ መጥተው እዚሁ ቀሩ።

ታዲያ አገሬው አሜሪካኖች መጤ በብዛት መስፈሩን አልወደዱትም ነበር። አንድም የብዙዎቹን ከአይርላንድ እና ከጀርመን የፈለሱት መጤዎች ተከታዮች የካቶሊክ ክርስትና እምነት ባለ መውደድ ሲሆን እስያውያኑን ደግሞ ወንጀለኞች ሴትኛ አዳሪዎች ወይም ደግሞ ሥራችንን ይሻማሉ ብለው ይጠሉዋቸው ነበር።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

የዩናይትድ ስቴትስ የኢሚግሬሽን ሕግ ታሪክ
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:29 0:00

XS
SM
MD
LG