ዋሺንግተን ዲሲ —
በቴሌቪዥን ፕሮግራሙ ዓለምቀፍ ዝናን ያተረፈው እና የምግብ አሰራር መጽሐፍት ደራሲው የሥድሳ አንድ ዓመቱ አንተኒ ቦርዴይን ዛሬ ዓርብ ፈረንሳይ ውስጥ ሞቶ ተገኘ።
አንተኒ ቦርዴይን በዓለም ዙሪያ እየተዘዋወረ የምግብ አሰራር ባህሎችን ለሚያስተዋውቅበት “ፓርትስ አኖውን” በተሰኘው የሲኤንኤን ቴሌቭዥን ተከታታይ ፕሮግራሙ ፈረንሳይ ስትራትስቡርግ ከተማ እንዳለ የምግብ ሥራ ባለሞያ ከሆነው ጓደኛው ኢሪክ ሪፐርት ህይወቱ አልፎ እንዳገኘው ሲኤንኤን አረጋግጧል።
የራሱን ህይወት አጥፍቶ መሆኑንም ሲኤንኤን አስታውቋል።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ