በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በቡድን 20ው ስብሰባ ዩናይትድ ስቴትስና ካናዳ በዩክሬን ጦርነት ሩሲያን አወገዙ


የሩሲያ ምክትል የገንዘብ ሚኒስትር ቲሙር ማክሲሞቭ በቡድን-20 የገንዘብ ሚኒስትሮች እና የማዕከላዊ ባንክ ገዥዎች ስብሰባ ላይ ባሊ፣ ኢንዶኔዥያ፤ እአአ ሐምሌ 15/2022
የሩሲያ ምክትል የገንዘብ ሚኒስትር ቲሙር ማክሲሞቭ በቡድን-20 የገንዘብ ሚኒስትሮች እና የማዕከላዊ ባንክ ገዥዎች ስብሰባ ላይ ባሊ፣ ኢንዶኔዥያ፤ እአአ ሐምሌ 15/2022

ዛሬ ዓርብ ኢንዶኔዥያ ላይ በተካሄደው የቡድን 20 አባል አገራት የውጭ ጉዳይ የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ የተካፈሉት የምዕራባውያን የፋይናንስ ሚኒስሮች የሩሲያ ባለሥልጣናት በዩክሬኑ ጦርነት በተፈጸሙት ግፎች ተባባሪ ናቸው ሲሉ ከሰዋቸዋል፡፡

የሞስኮ ከፍተኛ ዲሎማለት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ ስብሰባ ረግጠው ከወጡ ሳምንት በኋላ፣ ለሁለት ቀናት በኢንዶኔዥያው ባሊ ደሴት የተጀመረው ስብሰባ፣ ለገበያዎች መቀዛቀዝ፣ ለምግብ ዋጋ መናር፣ በፍጥነት ለተተኮሰው የዋጋ ግሽበት ምክንያት የሆነው የሩሲያው ወታደራዊ ወረራ ጥላውን ያጠለባት መሆኑ ተመልክቷል፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ የገንዘብ ሚኒስትር ጃኔት የሊን “በዓለም አቀፉ ምጣኔ ሀብት ላይ ለተስፋፋው አሉታዊ ቀውስ ሩሲያ ብቸኛው ተጠያቂ ናት” ሲሉ በስብሰባው መክፈቻ ላይ፣ ለሩሲያ ልኡካን መናገራቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ባለሥልጣናት ገልጸዋል፡፡

የሊን “የሩሲያ ባለሥልጣናት ለፑቲን አገዛዝ እየሰጡ ባሉት ድጋፍ ለጦርነቱ አሰቃቂ መዘዝ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡ ለንጹህና ህይወት መጥፋት ኃላፊነቱን ትጋራላችሁ” ማለታቸው ተዘግቧል፡፡

ሚኒስትሯን በመደገፍ የካናዳ ገንዘብ ሚኒስትር ክሪስቲያ ፍሪላንድ ፣ ለሩሲያ ልኡካን ወረራውን በመደገፋቸው በዩክሬን ለተፈጸመው “የጦር ወንጀል” ኃላፊነት ያለባቸው መሆኑን እንደነገሯቸው የካናዳ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል፡፡

የሩሲያ እና የዩክሬን የገንዘብ ሚኒስትሮች በስብሰባው በበይነ መረብ መሳተፋቸው ተመልክቷል፡፡

XS
SM
MD
LG