በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የፑቲንን ውሳኔ ተከትሎ ምዕራባዊን ሀገራት ለአዲስ ማዕቀብ እየተሰናዱ ነው


ፎቶ ፋይል፦ በሰሜን ጀርመን በሉብሚን አካባቢ የጋዝ መተላለፊያ መስመር እአአ 2/22/2022
ፎቶ ፋይል፦ በሰሜን ጀርመን በሉብሚን አካባቢ የጋዝ መተላለፊያ መስመር እአአ 2/22/2022

የሩሲያው ፕሬዚደንት ቭላድሚር ፑቲን በሩሲያ እጅ ውስጥ ያሉ ዶኔስክ እና ሉሃንስክ የተባሉ የምስራቅ ዩክሬን ስፍራዎችን እንደ ነጻ ሀገር ዕውቅና ለመስጠት መወሰናቸውን ተከትሎ ዩናይትድ ስቴትስ እና እንግሊዝ ተጨማሪ ማዕቀብ ይጥላሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው።

ዝርዝር ማብራሪያ ከመስጠት የተቆጠቡ አንድ የዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ ባለሥልጣን ለጋዜጠኞች ሲናገሩ “ሩሲያ ዓለም አቀፍ ህግን፣ የዩክሬንን ሉዓላዊነት እና የግዛት ክብር፣ የገዛ ራሷን ዓለም አቀፍ ግዴታዎች በመጣሷ ተጠያቂ ትሆናለች’’ ብለዋል ዘጋቢዎችን በስልክ ሲያናግሩ።

የብሪታኒያ የውጭ መስራቤት ኃላፊ ሊዝ ተርስ፣ የሀገራቸውን መንግሥት ቀጣይ እርምጃዎች ለመግለጽ ተመሳሳይ ቋንቋ የተጠቀሙ ሲሆን፣ የፈረንሳይ እና የጀርመን ተወካዮችም ጠንከር ያለ እርምጃ እንዲታቀድ በጸጥታው ምክር ቤት የትናንት ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን የመጀመሪያ ደረጃ ማዕቀቦችን በትናንትናው ዕለት ይፋ አድርገዋል።

በሩሲያ ዕውቅና በተሰጣቸው ስፍራዎች አሜሪካዊያን አዲስ ማዋለ ንዋይ እንዳይፈሱ፣ የንግድ እና የፋይናንስ እንቅስቃዎችን እንዳያደርጉ ማዕቀቡ ይከለክላል ።

XS
SM
MD
LG