አዲስ አበባ —
በትግራይ ክልል ካሉ ዩኒቨርሲቲዎች እና ከወልዲያ ዩኒቨርሲቲ በአማራ ክልል ወዳሉ ሦስት ዩኒቨርሲቲዎች የተመደቡ ተማሪዎች እስካሁን መፍትሔ አላገኘንም አሉ።
ተማሪዎቹ ቅሬታቸውን ለማሰማት ወደ ትምህርት ሚኒስቴር በተደጋጋሚ ቢያመሩም መልስ የሚሰጣቸውን አካል እንዳላገኙ ተናግረዋል፡፡
ተማሪዎቹ አሁን ላይ ለስነልቦና እና ለሌሎች ችግሮች መጋለጣቸውንም ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል፡፡ ከሚኒስቴሩ ምላሽ ለማግኘት የተደረገው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም፡፡