በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በመካከለኛው ምሥራቅና በአፍሪካ ከአራት ሕፃናት አንዱ በድኅነት ውስጥ ይኖራል - ዩኒሴፍ


ፎቶ ፋይል
ፎቶ ፋይል

የተባበሩት መንግሥታት የሕፃናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ ከትናንት በስቲያ ባወጣው አዲስ ሪፖርት በመካከለኛው ምሥራቅና በሰሜን አፍሪካ ሀገሮች ከአራት ልጆች አንዱ እንደ ንፁህ ውሃና ተገቢ መጠለያ የመሳሰሉ እጅግ መሠረታዊ የሆኑ አቅርቦቶችን አጥተው በድኅነት እንደሚኖሩ አመለከተ።

የተባበሩት መንግሥታት የሕፃናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ ከትናንት በስቲያ ባወጣው አዲስ ሪፖርት በመካከለኛው ምሥራቅና በሰሜን አፍሪካ ሀገሮች ከአራት ልጆች አንዱ እንደ ንፁህ ውሃና ተገቢ መጠለያ የመሳሰሉ እጅግ መሠረታዊ የሆኑ አቅርቦቶችን አጥተው በድኅነት እንደሚኖሩ አመለከተ።

አሥራ አንድ የአረብ ሃገሮችና አካቶ የተካሄደው ጥናት ሃያ ዘጠኝ ሚሊዮን ሕፃናት ሁለት ወይም ከሁለት በላይ በቂ የተመጣጠነ ምግብ፣ መሠረታዊ ትምህርት፣ የንፅህናና የመረጃ አቅርቦት የመሣሳሉ ለሕይወት እጅግ መሠረታዊ ፍላጎቶች በማያገኙበት የድኅነት አረንቋ ይኖራሉ ብሉዋል።

የወጣቶች ደኅነት ዓይነተኛ ምክንያት የትምህርት ዕጥረት መሆኑን ስለአካባቢዎቹ የልጆች ደኅነት የተጠናቀረ የመጀመሪያ የሆነው ይህ መረጃ አመልክቷል።

የትምህርት ዕድል ባላገኙ የቤተሰብ አባላት የሚመሩ ቤተሰቦች ውስጥ የሚኖሩ ልጆች በድኅነት የመኖር ዕድላቸው ዕጥፍ መሆኑን ያመለክታል። በዚህ ዓይነት ከሚኖሩ ዕድሜአቸው ከአምስት እስከ አስራ ሰባት ዓመት ከሆኑ ልጆች ውስጥ አንድ አራተኛው ትምህርት ቤት ያልገቡ ወይም ከዕኩዮቻቸው በሁለት ክፍል ወደኋላ የቀሩ ናቸው ብለዋል።

የዩናይትድ ስቴትስ የመካከለኛ ምሥራቅ እና የሰሜን አፍሪካ አካባቢ ድሬክተር ገርት ካፔሌሬ ሲናገሩ የልጆች ድኅነት አመዛኙ ምክንያት የቤተሰብ ገቢ ማነስ ሳይሆን ጥራት ያለው ትምህርት የጤና ጥበቃ መኖሪያና ንፁህ ውሃ ዕጦቱ ነው ብለዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG