በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ተመድ በኤርትራ የሚገኘው የስደተኞች ሰፈር እንዳይዘጋ ጥሪ አቀረበ


map eritrea and red sea
map eritrea and red sea

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰደተኞች አገልግሎት ኤርትራ “ኡምኩሉ” የተባለውን በሀገሪቱ አንድ ብቻ የሆነውን የስደተኞች ሰፈር እንዳትዘጋ ጥሪ አቅርቧል። የስደተኞቹ አገልግሎት ይህን ጥሪ ያቀረበው የአካባቢው ባለሥልጣኖች ስደተኞች ከእምኩሉ እንዲወጡ በማዘዛቸው ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ በመቶዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ከሰፈሩ ከወጡ በኋላ መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰደተኞች አገልግሎት በዌብሳይቱ ጠቁሟል።

ኡምኩሉ የሰደተኞች ሰፈር ከምፅዋ ወደብ ወደ 10 ኪሎ ሜትር ርቆ የሚገኝ ሲሆን ከሰኔ ወር አንስቶ ከ2,100 በላይ የሚሆኑ የሶማሊ ስደተኞች ተጠልለውበት ነበር። ከነሱም 1,300 የሚሆኑት አሁን ሰሜን ኢትዮጵያ መግባታቸውን የሰደተኞቹ አገልግሎት ዘገባ ጠቅሷል።

ለ20 ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ የሶማሊ ስደተኞችን ሲያስተናግድ የቆየውን ሰፈር ሌላ አማራጭ ሳያቀርቡ መዝጋት ከባድ ሥጋት ያስድራል ሲሉ በአፍሪካ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰደተኞች አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ራኦፍ ማዞ አስገንዝበዋል።

የስደተኞቹ አገልግሎት 1,300 የሚሆኑትን ከኤርትራ ወደ ትግራይ የገቡትን ሶማሊ ስደተኞችን በሀገሪቱ ደቡባዊ ክልል በሚገኘው መልካዲዳ ለማስፈር ከኢትዮጵያ ባለሥልጣኖች ጋር እያስተባበሩ መሆኑን ዘገባው ጠቅሷል።

ኢትዮጵያ ውስጥ 257,000 የሚሆኑ የሶማሊ ስደተኞች እንዳሉ የስደተኞቹ አገልግሎት ዘገባ ገልጿል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG