በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ተመድ፡-የህንድና የፓኪስታን መሪዎች ንግግር


ዛሬ ዓርብ የህንድ እና የፓኪስታን መሪዎች በኒውዮርክ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ንግግር ያደርጋሉ፡፡ ጃሙና ካሽሚር ውስጥ እየተቀጣጠለ ያለው ውጥረት ዓለምቀፍ ትኩረት ያገኛል ተብሎ ይጠበቃል።

የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ኻህን ከባድ መቅሰፍት ከመከሰቱ አስቀድሞ ዓለምቀፉ መድረክ፣ ፈጥኖ ለቀውሱ ምላሽ ይሰጣል ብለው እንደሚጠብቁ ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው ሻህ ማህሙድ ኩራሼ የገለፁት።

ባለፈው ግንቦት ወር በድጋሚ ከተመረጡ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በተመድ የተገኙት የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኒራንድራ ሞዲም ለጠቅላላ ጉባኤው ንግግር ሲያደርጉ ይህ በአምስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ የመጀመሪያቸው ነው የሚሆነው።

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕን ጨምሮ የተለያዩ መሪዎች ሁለቱ ሃገሮች ውዝግባቸውን በንግግር እንዲፈቱ ኣሳስበዋቸዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG