አዲስ አበባ —
በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤትና የአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው፡፡
የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤትና የአፍሪካ ሕብረት የምክክር ስብሰባ ጷግሜ 2 እና 3/2009 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሶማሊያና ደቡብ ሱዳን ጨምሮ አካባቢያዊ የፀጥታ ጉዳዮች፣ በአፍሪካ ሲካሄዱ የመጀመሪያ የሆነው የዚህ ስብሰባ ዋነኛ አጀንዳዎች እንደሚሆኑም ጠቁሟል፡፡
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ መለስ አለም ዛሬ ለጋዜጠኞች እንደገለፁት፣ የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ጥበቃ ምክር ቤትና የአፍሪካ ሕብረት የጋራ ስብሰባ ከኒው ዮርክ ውጭ ሲካሄድ ይህ የመጀመሪያው ይሆናል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ