በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

“መካከለኛ አፍሪካ ውጊያው ማገርሸቱ የማስጠንቀቂያ ደወል ነው” - ተመድ


ፎቶ ፋይል
ፎቶ ፋይል

መካከለኛ አፍሪካ ሪፐብሊክ ውስጥ ውጊያው ማገርሸቱ ከባድ ማስጠንቀቂያ ደወል የሚያሻው ነው ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር አሳሰቡ።

መካከለኛ አፍሪካ ሪፐብሊክ ውስጥ ውጊያው ማገርሸቱ ከባድ ማስጠንቀቂያ ደወል የሚያሻው ነው ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር አሳሰቡ።

ባልፈው ሳምንት በሀገሪቱ በሙስሊሞችና ክርስቲያኖች መካከል በተቀሰቀሰ ውጊያ ከመቶ የሚበልጡ ሰዎች ሲሞቱ በሺዎች የተቆጠሩ ከቀያቸው ተሰደዋል።

ትናንት የመንግሥታቱ ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ዜይድ ራአድ አል ሁሴን በሰጡት መግለጫ አንዳንዶቹ የሀገሪቱ የገጠር አካባቢዎች ወደተባባሰ ብጥብጥ እያሽቆለቆሉ መሄዳቸው በዋና ከተማዋ ባንጊ እና በሌሎችም ትላልቆቹ ከተሞች በመከራ የተገኘውን አንፃራዊ መረጋጋት አደጋ ላይ ይጥላል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG