በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኤርትራ መንግሥት በሰብዕና ላይ በተፈፀሙ ወንጀሎች እንዲከሰስ ተጠየቀ


ផូស៊ីល​ត្រី​ដែល​មាន​សណ្ឋាន​ដូច​​ជា​ត្រី piranha ដែល​ទើប​រក​ឃើញ​នៅ​សមុទ្រ Jurassic។ ត្រី​នេះ​​មាន​ធ្មេញ​មុត​​ស្រួច​​ដែល​ប្រហែល​សម្រាប់​ស៊ី​ព្រុយ​ត្រី​ប្រភេទ​ផ្សេង​ទៀត​។ ផូស៊ីល​ត្រី​នេះ​ត្រូវ​បាន​រក​​ឃើញ​នៅ​ខាង​ត្បូង​ប្រទេស​អាល្លឺម៉ង់​ដែល​មាន​អាយុកាល​តាំង​ពី​សម័យ​ដាយណូស័រ និង​​សត្វ Archaeopteryx។ ផូស៊ីល​នេះ​ត្រូវ​បាន​គេ​បង្ហាញ​ជា​រូបភាព​​នៅ​ទីក្រុង Eichstaett រដ្ឋ​សហព័ន្ធ Bavaria ប្រទេស​​អាល្លឺម៉ង់។
ផូស៊ីល​ត្រី​ដែល​មាន​សណ្ឋាន​ដូច​​ជា​ត្រី piranha ដែល​ទើប​រក​ឃើញ​នៅ​សមុទ្រ Jurassic។ ត្រី​នេះ​​មាន​ធ្មេញ​មុត​​ស្រួច​​ដែល​ប្រហែល​សម្រាប់​ស៊ី​ព្រុយ​ត្រី​ប្រភេទ​ផ្សេង​ទៀត​។ ផូស៊ីល​ត្រី​នេះ​ត្រូវ​បាន​រក​​ឃើញ​នៅ​ខាង​ត្បូង​ប្រទេស​អាល្លឺម៉ង់​ដែល​មាន​អាយុកាល​តាំង​ពី​សម័យ​ដាយណូស័រ និង​​សត្វ Archaeopteryx។ ផូស៊ីល​នេះ​ត្រូវ​បាន​គេ​បង្ហាញ​ជា​រូបភាព​​នៅ​ទីក្រុង Eichstaett រដ្ឋ​សហព័ន្ធ Bavaria ប្រទេស​​អាល្លឺម៉ង់។

የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ በመንግሥታቸው ላይ የተነገረውን ውንጀላ ውድቅ አድርገዋል፡፡

የኤርትራ መንግሥት ለሩብ ምዕት ዓመት ያካሄደው የተስፋፋና የተደራጀ የሰብዓዊ መብቶች ረገጣ በሰብዕና ላይ የተፈፀሙ ወንጀሎችን ያህል ነው ሲል በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የተቋቋመው የኤርትራ ሰብዓዊ መብቶች አያያዝ አጣሪ ኮሚሽን ከስሷል፡፡ ኮሚሽኑ ያወጣው ሪፖርት ዛሬ፤ ረቡዕ ሰኔ 1/2008 ዓ.ም ይፋ የተደረገው ጄኔቫ ላይ ነው፡፡

ኤርትራ “ነፃ የፍርድ ሥርዓት፤ ብሄራዊ ሸንጎ ወይም የተወካዮች ምክር ቤትና ዴሞክራሲያዊ ተቋማት የሌሉባት አምባገናዊ ግዛት ነች” ብለዋል የመንግሥታቱ ድርጅት የሰየማቸው የኤርትራ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ አጣሪ ኮሚሽነሮች፡፡ “በሕዝቡ ውስጥ ፍርሃት ለማስረፅና የፖለቲካ ተቃውሞን ለመገደብ ሲባል የባርነት አያያዝ፤ እሥራት፣ ደብዛ ማጥፋትና ሌሎችም ኢሰብዓዊ ወንጀሎች ተፈፅመዋል” ብለዋል ኮሚሽነሮቹ፡፡

“በድብቅ ሥፍራዎች ውስጥ የሥቃይ አያያዝ፣ መድፈርና ግድያን የመሳሰሉ ረገጣዎች እንደሚካሄዱ፤ ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ውስጥ በሃገሪቱ የብሄራዊ አገልግሎት ሥርዓት ውስጥ ዕድሜ ልካቸውን እንዲያገለግሉ የተበየነባቸው በግምት ከሦስት መቶ ሺህ እስከ አራት መቶ ሺህ የሚሆኑ ሰዎች ወደ ባርነት እንዲገቡ ተደርገዋል” ሲሉ የኮሚቴው ሊቀመንበር ማይክ ስሚዝ ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡ ሪፖርቱን “ሙሉ በሙሉ የተበላሸ፣ ወይም የተዛባ፤ ሙያዊ ጥራት የሌለውና የአንድ ወገን ሃሣብን ብቻ የያዘ ነው” ሲሉ የኤርትራ ፕሬዚዳንት አማካሪ የማነ ገብረአብ አጣጥለውታል፡፡ የማስረጃ ዶሴዎችን ማሰባሰባቸውን የሚናገሩት መርማሪዎች ግን የኤርትራን ጉዳይ ወደ ዓለምአቀፉ የወንጀል ችሎት እንዲመራ ለመንግሥታቱ ድርጅት የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

የኤርትራ መንግሥት በሰብዕና ላይ በተፈፀሙ ወንጀሎች እንዲከሰስ ተጠየቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:35 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG