በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኮቪድ መብት መርገጫ እንዳይሆን


ፎቶ ፋይል፦ የተባበሩት መንግሥታት ደርጅት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ሚሼል ባሽሌ
ፎቶ ፋይል፦ የተባበሩት መንግሥታት ደርጅት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ሚሼል ባሽሌ

መንግሥታት የኮሮናቫይረስን ወረርሽኝ ለመቆጣጠር ሲሠሩ ሰብዓዊ መብቶችን እያከበሩ እንዲሆን የተባበሩት መንግሥታት ደርጅት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ዛሬ ጥሪ አሰምተዋል።

“በልዩ ሁኔታ የሚታይ” ወይም “የአስቸኳይ ጊዜ እርምጃ” በሚል ሰበብና ሽፋን ሰብዓዊ መብቶች እንዳይደፈሩ የመንግሥታቱ ድርጅት ከፍተኛ ኮሚሽነር ሚሼል ባሽሌ በአፅንዖት አሳስበዋል።

“የአስቸኳይ ጊዜ ሥልጣናት ሊሠሩ የሚገባቸው ወረርሽኙን በተሳካ ሁኔታ ለመጋፈጥና ለመቆጣጠር ጉዳይ ብቻ ነው ሊሆን የሚገባው፤ አንዲት ነቁጥ ወደፊት፣ አንዲት ነቁጥ ወደኋላ ሊንፏቀቅ ጨርሶ መፈቀድ የለበትም፡፡ መንግሥታት ተቃውሞን እንዲጨፈልቁ፣ ሕዝብን ጨምድደው እንዲቆጣጠሩ፣ ወይም ሥልጣን ላይ ለመቆየት ከጅለው የሚጠቀሙበት መሣርያ ሊሆን ከቶ አይገባም” ብለዋል ኮሚሽነር ባሽሌ።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

ኮቪድ መብት መርገጫ እንዳይሆን
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:20 0:00


XS
SM
MD
LG