በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የተመድ ዋና ጸሃፊ በሦስት አፍሪካ አገሮች የሲቪል አስተዳደር እንዲመለስ አሳሰቡ


የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ፤ የሴኔጋል ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል በምዕራብ አፍሪካ ጉብኝታቸው በፕሬዚዳንታዊ ጽ/ቤታቸው በዳካር ያደረጉላቸው አቀባበል እአአ ግንቦት 1/2022
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ፤ የሴኔጋል ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል በምዕራብ አፍሪካ ጉብኝታቸው በፕሬዚዳንታዊ ጽ/ቤታቸው በዳካር ያደረጉላቸው አቀባበል እአአ ግንቦት 1/2022

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ ትናንት እሁድ ባደረጉት ጥሪ፣ በቡርኪና ፋሶ፣ ጊኒና ማሊ የሚገኙ አምባገነን መሪዎች ሥልጣንን ለሲቪሎች በአስቸኳይ እንዲያስረክቡ አሳሰቡ፡፡

ዋና ጸሃፊው ይህን ያሳሰቡት፣ ከሴኔጋል ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል ጋር፣ በዳካር ተገናኝተው ከተነጋገሩ በኋላ ነው፡፡

ጉተሬዥ ህገ መንግሥታዊ ሥርዓት ወደ ቦታው እንዲመለስ፣ ሥልጣንን ያላግባብ ከጨበጡ ከሶስቱ አገራት መሪዎች ጋር በቀጣይነት ለመነጋገር መስማማታቸውንም አስታውቀዋል፡፡

ከጅሃዲስቶቹ አማጽያን ጋር በሚያደርጉት ትግል፣ ችግር ውስጥ መሆናቸው የሚታወቁት ሦስቱ የሳህል አገሮች፣ ማሊ፣ ጊኒንና ቡርኪናፋሶ፣ በቅርቡ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ተካሂዶባቸዋል፡፡

የሴኔጋሉ ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል፣ ኤካዎስ የተባለው የምዕራብ አፍሪካ አገሮች ህብረት የወቅቱ ሊቀመንበር መሆናቸው ተመልክቷል፡፡

XS
SM
MD
LG