በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አንድነት በመንግሥት ላይ ክሥ አሰማ፤ ሪፖርት ሊያወጣ ነው


ዶ/ር ነጋሦ ጊዳዳ
ዶ/ር ነጋሦ ጊዳዳ

ባለፉ ሦስት ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ ሲፈፀሙ ቆይተዋል ያላቸውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችና በደሎችን የያዘ ሰነድ በቅርቡ እንደሚያወጣ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ አስታውቋል፡፡




አንድነት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ፓርቲ
አንድነት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ፓርቲ

please wait

No media source currently available

0:00 0:07:47 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ


ባለፉ ሦስት ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ ሲፈፀሙ ቆይተዋል ያላቸውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችና በደሎችን የያዘ ሰነድ በቅርቡ እንደሚያወጣ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ አስታውቋል፡፡

የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሦ ጊዳዳ ዛሬ ማምሻውን ከቪኦኤ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ካለፈው ሐምሌ እስከ መስከረም ባለው ጊዜ ከ150 በላይ የፓርቲያቸው አመራር አባላትና ደጋፊዎቻቸው መጠለፋቸውን፤ ያለአግባብ መታሠራቸውን መደብደባቸውንና እንግልትና ወከባ የደረሰባቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የአርትኦት ሥራዎች እንደተጠናቀቁ ሪፖርቱ በጥቂት ሣምንታት ውስጥ እንደሚወጣ፣ ፓርቲያቸው ለሃገር ውስጥ የፌደራልና መንግሥትና የክልሎች የሥልጣን አካላት፣ ለዓለምአቀፍም የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ተቋማትና ለመገናኛ ብዙኃን ቅጂዎችን እንደሚያደርሱ፣ በዌብ ሣይታቸው ላይም እንደሚያወጡት ዶ/ር ነጋሦ ገልፀዋል፡፡

“ተፈፅመዋል” የሚሏቸውን በደሎች አስመልክቶ ክሥ ይመሠርቱ እንደሆነ ዶ/ር ነጋሦ ሲጠየቁ እያንዳንዱን ጉዳይ ወደ ፍርድ ቤት ለመውሰድ አቅም እንደሌላቸው አመልክተው የፓርቲያቸው በሆኑ ጉዳዮች ላይ ግን ወደ ሕግ እንደሚሄዱ ጠቁመዋል፡፡

ዶ/ር ነጋሦ ጊዳዳ
ዶ/ር ነጋሦ ጊዳዳ
በሌላ በኩል ግን “… እስከአሁን ካለው ልምዳችን እንደምናውቀው ፍትሕ የለም፣ ፍትሕ አናገኝም፣ ዜጎች ፍትሕ አያገኙም፤ በተለይ በፖለቲካ ጉዳይ ችግር የደረሰባቸው፤ ወንጀል የተፈፀመባቸው ሰዎች፤ በተጨማም የማይሆን ፀረ-ሽብር ሕግ ወጥቶ ትክክል ባልሆነ ውንጀላ ከሽብርተኞች ጋር ግንኙነት አላችሁ፤ እናንተ ሽብርተኛ ድርጅቶችን የሚደግፍ ድርጅት አባል ናችሁ እየተባሉ የሚንገላቱ፣ የሚታሠሩ ሰዎች አሉ፤ ይህ እየተከሰተ ያለው መንግሥት እያወቀው ነው፤ ፍርድ ቤቶችም አልረዱንም” ብለዋል ዶ/ር ነጋሦ፡፡

“በአንድነት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ግምገማና ዕምነት ኢትዮጵያ እያደገችና እየለማች ነው ወይስ አይደለም?” ተብለው የተጠየቁት የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሦ “ዜጎችን ሁሉ ያላሣተፈ ልማት ዕድገት አያመጣም፤ ሕንፃዎች እየተገነቡ ቢሆንም እኛ የምናውቀው ድሕነት እየበዛ መምጣቱን ነው” ብለዋል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝን ማስጠንቀቂያዎች አስመልክቶም ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲህ ዓይነት ውንጀላዎችን ባሰሙ ቁጥር የበታች ካድሬዎችና የመንግሥቱ ባለሥልጣናት በአባሎቻቸው ላይ የሚያደርሱትን ወከባ እንደሚያበረቱ ሊቀመንበሩ ተናግረዋል፡፡

ለአንድነት ክሦች ምላሽ ከመንግሥት አካላት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሣካም፡፡

ለተጨማሪ መረጃዎች የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
XS
SM
MD
LG