በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኢራቋ የኩርዶች ከተማ በሬስቶራንት ላይ በተፈፀመ ጥቃት የሰው ህይወት አለፈ


አንድ ታጣቂ፣ በኢራቋ የኩርዶች ከተማ አረቢል ውስጥ በሚገኝ ሬስቶራንት ውስጥ በዛሬው ቀን በፈፀመው ጥቃት፣ እስካሁን በተረረጋገጠው መሠረት አንድ የቱርክ ዲፕሎማት መገደሉን፣ መንግሥዊው የቱርኩ ዜና አውታር ዘግቧል።

መንግሥታዊው ዜና አገልግሎት እንደዘገበው፣ የቱርክ ምክትል ዋና ቆንስላ የነበረው ዲፕሎማት አረቢል ውስጥ በሚገኘው የቆንስላ ጽ/ቤት በሥራ ገበታው ላይ ነበር።

ሌሎች በርካታ ሰዎች መሞታቸውና መቁሰላቸው የተዘገበ ቢሆንም፣ እስካሁን ግን የሞቱትንም ሆነ የቆሰሉትን ሰዎች ቁጥር በትክክል ማወቅ አልተቻለም።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG