በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በቱኒዚያ ያሉ አፍሪካዊ ስደተኞች ወደ ሌላ አገር እንዲዛወሩ ጠየቁ


በአገሪቱ ወከባና እንግልት ይደርስብናል በሚል ከአንድ መቶ በላይ የሚሆኑ ጥገኝነት ጠያቂዎች በቱኒዚያ መዲና ቱኒዝ በሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጽ/ቤት በመሰባሰብ ወደ ሌላ አገር እንዲዛወሩ ጠይቀዋል፡፡

የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ካይስ ሳይድ ስደተኞችን ከነቀፉና፣ “የቱዚያውያንን ማንንነት ሊያጠፉ የመጡ ናቸው” ብለው ከተናገሩ በኋላ፣ ጥቃትና እንግልት እንደደረሰባቸው በአብዛኛው ከሱዳን የመጡትና በመንግሥታቱ ድርጅት ጽ/ቤት የተሰባሰቡት ስደተኞች ተናግረዋ፡፡

በቱኒዚያ ከጥቃት የሚጠብቃቸው እንደሌለና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና የአውሮፓ ሕብረት በሌላ ደህንነታቸው መጠበቅ የሚችልበት አገር መሥፈር እንዲችሉ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡

ስደተኞቹ ላለፉት 10 ቀናት በመንግሥታቱ ድርጅት ጽ/ቤት ተቃውሞ ሲያሰሙ ሰንብተዋል፡፡

ምዕራባውያንና አፍሪካውያን የቱኒዚያ ሸሪኮች ወቀሳ ካቀረቡ በኋላ፣ የቱኒዚያ መንግሥት ስደተኞቹ ጥቃት ሲገጥማቸው የሚያሳውቁበትን የስልክ መስመር እንዲሁም የጤናና የስነ ልቦና ድጋፍ ማግኘት የሚችሉበትን ሁኔታ አመቻችቷል ተብሏል፡፡

XS
SM
MD
LG