የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ ከካናዳ፣ ሜክሲኮ እና ቻይና በሚገቡ ምርቶች ላይ የጣሉት አዲስ ቀረጥ ተፈጻሚ ከመደረጉ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ከካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ጋር ዛሬ መነጋገራቸውን አስታወቁ።
‘ትሩዝ ሶሻል’ በተባለው የራሳቸው የማኅበራዊ ሚዲያ አውታር ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ ከሰአት በኋላ ላይ ትሩዶን እንደገና አነጋግራቸዋለሁ ያሉት ትረምፕ፤ አዲሱ ቀረጥ ካናዳ ወደ አሜሪካ የሚገባውን ለብዙ ህይወት መጥፋት ምክኒያት የሆነ ‘ፌንቲኔል’ የተባለ አደገኛ መድሃኒት ቁጥጥር እንድታጠነክር ለማስገደድ ነው ሲሉ ይሞግታሉ።
መድረክ / ፎረም