ዋሺንግተን ዲሲ —
ዶናልድ ትራምፕ የዩናይትድ ስቴትስ 45ኛ ፕሬዚዳንት ሆነው ከተመረጡ ስድሥት ወራት ሆኗል።
ትራምፕ ለፕሬዚዳንትነት የተመረጡት በአሜሪካ ታሪክ ከፍተኛ ክፍፍል ከታየባቸው የምርጫ ሂደቶች አንዱ በሆነው ነው።
ትራምፕ የተወዳደሩትም የፖለቲካ ትርምስ በመፍጠር ዘዴ ነው። ይሁንና እስካሁን ባለው ጊዜ በፕሬዚዳንትነት ዐብይ ሊባል የሚችል ሥራ ሲያከናውኑ አልታየም።
በቀድሞው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ አስተዳደር ወቅት ለሥምንት ዓመታት ያህል የዋይት ሃውስ አስተዳደርን ተቆጣጥረው የቆዩት ዲሞክራቶች በበኩላቸው አዲሱ ሚናቸው ምን እንደሚሆን እያሠላሰሉ ናቸው።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ