በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

"ፍተሃዊ፣ ዘመናዊና ህጋዊ" የአሜሪካን የኢሚግረሽን አካሄድ የሚቀይር ዕቅድ


የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ "ፍተሃዊ፣ ዘመናዊና ህጋዊ" ያሉትን የአሜሪካን የኢሚግረሽን አካሄድን የሚቀይር ዕቅደ ሃስብ ትናንት ይፋ አድርገዋል።

የሀገሪቱ ሁለት ዋናዎቹ ፓርቲዎች የምክር ቤት አባላት ግን፣ በምክር ቤት አዎንታ የማግኘት ዕድል የለውም ይላሉ።

“ፍልሰተኞችን በዘፈቀደ ማስገባት የአሜሪካን እሴት ይፃረራል። እዚህ ብዙ አስተዋፅዕ ሊያደርጉ የሚችሉ በርካታ ብቃት ያላቸው ሰዎችን ዕድል ያሳጣል” ሲሉ ፕሬዚዳንት ትረምፕ ትላንት ከሰዓት በኋላ በዋይት ኃውስ ተናግረዋል።

የፕሬዚዳንቱ የኢሚግርሽን ዕቅደ ሃሳብ ቤተሰብን ከማገናኘትና ከሰብዓዊ መለኪያዎች ወጥቶ በዓለም ዙርያ ያሉ ምርጥና ብልሆችን በማስገባት ላይ በሚያተኩር አሰራር እንዳሚለወጥ ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG