በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በዶር. ደብረ ጽዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን አቶ ጌታቸውን ከክልል ፕሬዚዳንትነት አንስቻለሁ አለ


የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል
የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል
በዶር. ደብረ ጽዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን አቶ ጌታቸውን ከክልል ፕሬዚዳንትነት አንስቻለሁ አለ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:53 0:00

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ፣ ከዛሬ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ከሥልጣን እንዲወርዱ ወስኛለሁ ሲል በዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው ህወሓት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

አቶ ጌታቸውን ጨምሮ በአወዛጋቢው ጉባኤ ያልተሳተፉ 13 የጊዜያዊ አስተዳደሩ የክልል እና የዞን አመራሮች በህወሓት ተመድበው ከነበሩበት ሥልጣን እንዲወርዱ ወስነናል በማለትም ነው መግለጫው ያስታወቀው።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዛሬ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ በነዶከተር ደብረ ጽዮን ላይ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ ብሏል፡፡

አስተዳደሩ በመግለጫው፣ ይህ ኃይል በዛሬው ዕለት በይፋ መፈንቅለ መንግሥት አወጇል ሲል ከሷል።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG