በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ቲለርሰን የሥድስት ቀን የላቲን አሜሪካ ሀገሮች ጉብኝታቸውን ጀመሩ


የዩናይትድ ስቴትሱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን
የዩናይትድ ስቴትሱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን

የዩናይትድ ስቴትሱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን፣ የሥድስት ቀን የላቲን አሜሪካ ሀገሮች ጉብኝታቸውን ዛሬ ሐሙስ ጀመሩ። ሚስተር ቲለርሰን በዚህ ጉብኝታቸው፣ በቀውስ በተመታችው ቬኔዙዌላ ዴሞክራሲያዊ ለውጦች እንዲካሄዱ የክልሉ መንግሥታት ጫና እንያደርጉ ያሳስባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የዩናይትድ ስቴትሱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን፣ የሥድስት ቀን የላቲን አሜሪካ ሀገሮች ጉብኝታቸውን ዛሬ ሐሙስ ጀመሩ። ሚስተር ቲለርሰን በዚህ ጉብኝታቸው፣ በቀውስ በተመታችው ቬኔዙዌላ ዴሞክራሲያዊ ለውጦች እንዲካሄዱ የክልሉ መንግሥታት ጫና እንያደርጉ ያሳስባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የሥድስቱ ቀናት የቲለርሰን ጉዞ ወደ ሜክሲኮ፣ አርጀንቲና፣ ፔሩ፣ ኮሎራዶ እና በመጨረሻ ጃማይካ እንደሚወስዳቸው ታውቋል።

አንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሥልጣን እንደተናገሩት፣ ዩናይትድ ስቴትስ የቬኔዙዌላን ሁኔታ ለማርገብ ዲፕሎማሲያዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ መንገዶችን ሁሉ ትጠቃማለች።

ቬኔዙዌላ በከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውስ ውስጥ ከገባች እነሆ አምስተኛ ዓመቷን ይዛለች።

ባለፈው የአውሮፓውያኑ ጥር ወር፣ የዩናይትድ ስቴትስ የገንዘብ ሚኒስቴር፣ ቀደም ብሎ በማዕቀብ መዝገቡ ውስጥ በነበሩት ላይ፣ “በከፍተኛ ሙስና የተዘፈቁ ናቸው” ባሏቸው ሌሎች አራት ወታደራዊ ባለሥልጣናት ላይ፣ ማዕቀብ መጣሉ ይታወቃል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG