ዋሺንግተን ዲሲ —
ኩባ ባሉ የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ሰራተኞች ላይ የተፈጸሙ ጤና ተኮር ጥቃቶችን ለመመርመር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን የተጠያቂነት መርማሪ ቦርድ እንደሚጠሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ዛሬ ገልጿል።
ሴነተሮች ስለተባለው ጥቃት በተነጋገሩበት ወቅት ዲሞክራቶችና ሪፖብሊካውያን ሴነተሮች በቂ የምርመራ ጥረት አልተደረገም በማለት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለሥልጣኖችን ነቅፈዋል።
ቲለርሰን “ዒላማ ያደረጉ ጥቃቶች” ባሉት ምክንያት ሀቫና ያሉ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችና ሌሎች የጆሮ መደፈን፣ የማዞር፣ የማቅለሽለሽና የድካም ስሜት እየተሰማቸው ነው።
ኩባ ይህን ለማስከተል ያደረግኩት ነገር የለም ስትል አስተባብላለች።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ