በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሽረ መምህራን ደመወዝ ካልተከፈላቸው ሥራ እንደሚያቆሙ አስጠነቀቁ


በሽረ መምህራን ደመወዝ ካልተከፈላቸው ሥራ እንደሚያቆሙ አስጠነቀቁ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:59 0:00

በሽረ መምህራን ደመወዝ ካልተከፈላቸው ሥራ እንደሚያቆሙ አስጠነቀቁ

ለሁለት ዓመታት በዘለቀው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ምክንያት፣ የ17 ወራት ደመወዛቸው እንዳልተከፈላቸው የገለጹ፣ በትግራይ ክልል የሽረ እንዳሥላሴ ከተማ መምህራን፣ ውዝፍ ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው፣ ትላንት እሑድ ባካሔዱት ሰላማዊ ሰልፍ ጠየቁ፡፡

ጥያቄያቸው ካልተመለሰ፣ ሥራ የማቆም ውሳኔ ሊያሳልፉ እንደሚችሉ፣ መምህራኑ አስጠንቅቀዋል፡፡የትግራይ ክልል መምህራን ማኅበር በበኩሉ፣ ሰልፍ የወጡ መምህራን ያሰሙት አቤቱታ፣ “በክልሉ የሚገኙ የ45 ሺሕ መምህራን ጥያቄ እንደኾነ ገልጾ፣ አስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጣቸው አመልክቷል፡፡ በጉዳዩ ላይ፣ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG