በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ዶሮ አርቢ አሜሪካውያን ባለሃብቶች በትግራይ


የተሻሉ የዶሮ ዝርያዎች
የተሻሉ የዶሮ ዝርያዎች

ዴቪድ ኤልስ እና ትረንት ኮስቶቮስ የተባሉ አሜሪካውያን ባለሃብቶች ትግራይ፤ መቀሌ ከተማ ውስጥ በሚገኝ የመቀሌ ማዕከል ከህንድ የተገኙ የተሻሉ የዶሮ ዝርያዎችን በዘመናዊ መንገድ በማራባት ላይ ተሠማርተዋል::

ዘንድሮ ግማሽ ሚልዮን የዶሮ ጫጩቶችን ወደ ሞዴል ገበሬዎች ለማዳረስ ተዘጋጅተዋል::

ይህንን ቁጥር በሚቀጥለው ዓመት ወደ አንድ ሚልዮን ከፍ ለማድረግ ማቀዳቸውን ገልፀው “በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት እያንዳንዷ የትግራይ እናቶች ሰላሣ ዶሮዎች እንዲኖሯት እናስችላለን” ብለዋል ዴቪድ ኤልስ::

ትረንት ኮስቶቮስ “እኛ እየሠራን ያለነው በምሳሌነት የሚጠቀስ ማኅበረሰባዊ መዋዕለ-ነዋይን በተግባር ለማሣየት ነው” ይላሉ::

የመቀሌ እርሻ ለረጅም ዓመታት በሞያዊ ክፍተትና በአስተዳደራዊ አቅም ማነስ የሚፈለገውን ውጤት ሳያስመዘግብ መቆየቱን በዚህም መንግሥት በዓመት 15 ሺህ ዶሮዎችን ብቻ ያመርትበት እንደነበርም ለማወቅ ተችሏል::

XS
SM
MD
LG