መቀሌ —
"ጦርነት ለማስቀረት ስንል ኃይል በማጠናከር ተዘጋጅተናል" ብለዋል የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል።
"የፌደራል መንግሥት ሥልጣን የያዘ ሃይል በትግራይ ህዝብ ላይ ሲፈፅመው የነበረውን ሴራ ወደ ኃይል እርምጃ በማሸጋገር ላይ ስለሆነ የክልሉ ህዝብ ዝግጅቱን አጠናክሮ መቀጠል አለበት" ብለዋል ለክልሉ መገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ።
የሀገሪቱን ችግር ለመፍታት ሁሉን አቀፍ መድረክ መዘጋጀት አለበት ሲሉ አክለዋል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡