በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

“አሥተምር .. አሰልጥን .. አገልግል” - የበጎ ፈቃድ አገልግሎትና መንገድ ጥቆማ


አቶ ሳምሶን ደምሴ ተፈራ እና ዶ/ር ያዕቆብ አስታጥቄ
አቶ ሳምሶን ደምሴ ተፈራ እና ዶ/ር ያዕቆብ አስታጥቄ

"ትምሕርት ጨርሶ ሥራ የሚፈልግ ሳይሆን ሥራ ፈጣሪ የሚሆን ተማሪ ለማፍራት ልዩ ሥልጠና ይፈልጋል። ያን ነው ለማድረግ እየሰራን ያለነው።" ዶ/ር ያቆብ አስታጥቄ “አንድ መሥራች አባላችን እንደሚለው‘በገበሬው ግብር ክፍያ ተምረን ይህችን ያህል ለሃራችን መልሰን የመስጠት ኃላፊነት አለብን’ የሚለው ዓላማ ትልቁ ሆኖ ስላየነው ፈተናዎቹን ለማለፍ ረድቶናል። ቶሎ ተቀባይነት ማግኘት ያለመቻል ተስፋ ሊያስቆርጥ ይችላል.." አቶ ሳምሶን ደምሴ ተፈራ

በቅርቡ ነው ወደ አዲስ አበባ ተጉዘው በመጠነ ሠፊ የሞያ መስኮች የሥልጠና አገልግሎቶች ሰጥተው የተመለሱት። ሥማቸው በእንግሊዝኛ በአጽሕሮት ሲነበብ ተስፋ የሚል ድምጽ ይሰጣል። ለወገናቸው ተሥፋ መስጠት መፈለጋቸውን ለማመላከት የመረጡት መጠሪያ። መቶ ያህል የምሕንድስና ፋኩሊቲዎች፤ ሃያ ዘጠኝ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለተማሪዎችና ለመምሕራን ጭምር ልዩ ሥልጠናዎችን ሰጥተዋል።

ከመሥራች አባላቱ ሁለቱን አነጋግረናል። ዶ/ር ያቆብ አስታጥቄ በዩናይትድ ስቴትሱ ሞርጋን ስቴት ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ፕሮግራሞች ምክትል ፕሬዝዳንት እና የኤክትሪክ ምሕንድስና ትምሕርት መምሕር ሲሆኑ አቶ ሳምሶን ደምሴ ተፈራ በዩናይትድ ስቴትስ የሠራተኞችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍል ኃላፊ ናቸው። የበጎ ፈቃድ አገልግሎትና ጥናት ማሕበራቸው TASFA የውጭ ግንኙነት ጉዳዮች ተጠሪም ናቸው።

ሙሉውን ውይይት ከዚህ ይከታተሉ።

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ ጥናት እና መንገድ ጥቆማ
please wait

No media source currently available

0:00 0:14:37 0:00
“አሥተምር .. አሰልጥን .. አገልግል” - ክፍል ሁለት
please wait

No media source currently available

0:00 0:14:39 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG