ዋሽንግተን ዲሲ —
“ዓለምአቀፍ ጥምረት ለጣና ደኅንነት” የሚል ስያሜ ያለው ግብረሠናይ ድርጅት ለዋሽንግተን ዲሲና አካባቢዋ አዘጋጅቶ ባካሄደው "ጤና ለጣና" የተባለ ፕሮግራም ላይ ባሰባሰበው ገንዘብ ዘመናዊ የእንቦጭ ማጨጃ መሣሪያና የታጨደውን አረም ተሸክሞ ወደ ማጠራቀሚያ ወይም ማጓጓዣ ተሽከርካሪ ከሚወስደው ተዘዋሪ ቀበቶ ጋር መግዛቱን ገልጿል።
የክልሉን መንግሥት ወክለው በዩናይትድ ስቴትስ ቆይታ አድርገው የነበሩትን የአማራ ክልል የአካባቢ ደንና ዱር እንስሣት ጥበቃና ልማት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በላይነህ አየለን ስቱዲዮ ጋብዘን አነጋግረናቸዋል።
(ቃለ ምልልሱን ከተያይዘው የድምፅ ፍይል ያድምጡ)
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ